2013 ኦገስት 29, ሐሙስ



የሚስኪኖች አመጽ
ሀገር ምድሩ ሁሉ ተሸጦ በገንዘብ
የኛን ስፍራ ማጣት ህዝብ እንዴት ይገንዘብ፡፡
አላይ ላለ አይን ለማይሰማ ጆሮ
አመጽ አንስተናል ከዛሬ ጀምሮ
ካጣን ትንሽ ስፍራ ለመላወሻ እንኳን
ለሚሻግት እህል ማስጫ ከተቸገርን
ምንዱባን ተነሱ አብዮት አቃጥሉ
የደሀ ንብረት ነው የሐብታም ግዛት ሁሉ፡፡
ሰኔ 26/2005