2014 ጁላይ 3, ሐሙስ



yrzm H¥M

H¥¥T nW g!z@W =l¥ nW qn#

å¶T nW G²t$ XS„ nW {n#

xMNtET rFÄ*L mRGD mdlq$

>FN nW mQds# LwlqM ¥q$

mSqL xLwrdM kYs! xLtwgrM

                       x¥{ÃN nGsW g@¬ xLkbrMÝÝ 

                                                                   27/8/2006




         yg!z@ wdB
m¬mN Æì nW s!kBR xlQ§qE
XWqT JLnT nW s!gN x§êqE
y¸ÃyW xYñRM xÃg"M ¥rG
bzmn sRì ybql CFRG
l[/Y FQR ylM kng\ k#‰Z
mÄB kBé úl ï¬ ylM lxL¥Z
                              2/9/2006

2014 ጁን 23, ሰኞ

እውቀት እንደቀላል ሲጠፋ



ከንባታ ጠንባሮ አካባቢ በስራ ምክንያት ሔጄ ነበር፡፡ ህጻናት ማንበብን አዝናኝ በሆነ መንገድ እንዲማሩ እና እንዲወዱ የሚያደር ስልጠና ለመስጠት፡፡ ስልጠናው ላይ ለህጻናቱ ትምህርታዊ ጨዋታ በሙከራ ደረጃ ቀረበ፡፡ ጨዋታው በአንድ ካርድ ላይ የአንድ እንስሳ ስም በአማርኛ፣ በእንግሊዝኛ እና በከንባተኛ ይጻፋል፡፡ በሌላ ካርድ ደግሞ የእንስሳው ፎቶ ይቀመጣል፡፡ በዚህ ሁኔታ የተዛጋጁ በርከት ያሉ ምስሎችና ስሞችን በማገናኘት እንደካርታ ጨዋታ በመብላት ነጥብ ማስቆጠር ነው፡፡
በመሐል ያልጠበኩት ነገር ተከሰተ፡፡ ተማሪዎቹ የአንድ በጣም ታዋቂ እንስሳን ፎቶ ተመለከቱ፤ ሆኖም ከተጻፈው ስሙ ጋር ለማገናኘት ተቸገሩ፡፡ ግራ ስጋባ “ይህ እንስሳ ምንድን ነው” አልኳቸው ካርዱን ይዤ፡፡ ሁሉም በእርግጠኝነት እንደማያውቁት ነገሩኝ፡፡ ወጣቷን የልጆቹን መምህርት ጠራኋትና “ይሔ እንስሳ በአካበቢው ቋንቋ ምን ተብሎ እንደሚጠራ ለልጆቹ  ንገሪልኝ” ስል ትብብሯን ጠየቅኩ፡፡ መምህርቷም ስዕሉን እንዳየች ፊቷን አጨፈገገችና “ይሄን እንስሳ ስሙን አላውቀውም፡፡ ግን ሆሳዕና ስሄድ አይቼው አውቃለሁ” አለችኝ፡፡ አሁን በበለጠ በአግራሞት ተሞላሁ፡፡
“እስቲ አባባ ስሙን ሳያውቁት አይቀሩም ልጥራቸው” አለችና በእድሚያቸው ገፋ ያሉትን የትምህርት ቤቱ ሽማግሌ ስከትላ መጣች፡፡ እጄ ላይ ያለውን ስዕል እያሳየሁ የቀድሞውን ጥያቄ ጠየቅኳቸው፡፡ አዛውንቱ ፈገግ አሉና “የዚህ እንስሳ ስም ‘ውሺቾ’ ይባላል፡፡ ያው በአማርኛ ‘ውሻ’ የምትሉት ነው፡፡ ሆኖም በዚህ አካባቢ ውሻ ፈጽሞ አይታወቅም” አሉኝ፡፡
ምክንያቱን ለማወቅ ጓጉቼ ጠየቅኋቸው፡፡ “ከብዙ ዘመናት በፊት በኔ አያት ዘመን የውሻ በሽታ ገብቶ ህዝቡን ፈጀው፡፡ ብዙ ሰው አለቀ፡፡ በዚህ የተነሳ የሐገር ሽማግሌዎች ተሰበሰቡና ‘ውሻ ያሳደገ ውሻ ይውለድ፡፡ በአካባቢ ውሻ ያየ ሁሉ ውሻውን ያባርር’ በማለት አወጁ፡፡ በዚህም ተነሳ ውሻ ከሐገሩ ጠፋ፡፡ ስለዚህ የአካባቢው ህጻናት ብቻ ሳይሆኑ ወላጆቸው ጭምር ወደሌላ አካባቢ ካልሄዱ በቀር ውሻን አያውቁትም፡፡” በማለት አስረዱኝ፡፡  
እንደው እንደዘበት፣ እንደቀላል፣ ‘የሰው ልጅ የመጀመሪያ ወደጅ’ ተብዬው ውሻ መረሳቱ ብቻ አይደለም የደነቀኝ፤ እንዴት በቀላሉ ውሻን ያክል እውቀት ከሰው አምሮ ውስጥ እንደሚጠፋ ማወቄ ጭምር እንጂ፡፡ ከዚህ በላይ ግን አንድ ቁም ነገር መያዝ ፈለግኩ፡፡ የፈራ አለቃ ሁሉ ለጊዜያዊ መፍትሄ የሚወስደው ክልከላ ለትውልድ ትክክል መስሎ እውቀትን እንደሚጋርድ ማሳያ ይሆናል፡፡ ሐገሬ ደግሞ የዚህ አይነት ባህሪ የተጠናወታቸው ከላይ እስከታች ያሉ አለቆች ሞልተዋታል፡፡ ለዛሬ ችግር የትውልድን አዕምሮ የሚደፍኑ!!!